SUBSCRIBE

Search This Blog

Aug 10, 2020

ተጠያቂነት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሚና የተጠያቂነት መርህ ይዘትና ገፅታው



]ተጠያቂነት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሚና
የተጠያቂነት መርህ ይዘትና ገፅታው
የተጠያቂነት መርህ ውሳኔ ሰጪዎች በአንድ ጠያቂ አካል ፊት ቀርበው የድርጊታቸውን ህጋዊነት፣ ፍትሀዊነት እና ትክክለኛነት እንዲያስረዱ የሚጠየቁበት መንገድ ነው፡፡ ይህም በህግ ወይም በፓለቲካዊ የስልጣን ቁጥጥር ስልቶች ይተገበራል፡፡ ፖለቲካዊ ቁጥጥር በህግ አውጭው አማካይነት የሚደረግ ቁጥጥር ሲሆን ትኩረቱ የመንግስት ውሳኔዎች፣ ድርጊቶችና እንቅስቃሴዎች ፖለቲካዊ ተገቢነት መመርመርና በቅርበት መከታተል ነው፡፡a በዚህም መሰረት የመንግስት ባለስልጣናት በህግ አውጭው ፊት ቀርበው ውሳኔያቸው ወይም ድርጊታቸው ከፖሊሲ አቅጣጫዎች አንጻር ትክክለኛ እና አስፈላጊ መሆኑን ማስረዳት ይጠበቅባቸዋል፡፡
ህጋዊ ቁጥጥር በአንጻሩ በመደበኛ /ቤቶች እና በተወሰነ መልኩ በአስተዳደር /ቤቶች የሚደረግ የስልጣን ቁጥጥርን ይመለከታል፡፡ ህጋዊ ቁጥጥር የስልጣንን ህጋዊነትና ፍትሀዊነት ከማረጋገጥ ባለፈ የውሳኔውን ይዘት ማለትም ትክክለኛነት ወይም ተገቢነት አስመልክቶ ፍተሻ የሚደረግበት የቁጥጥር ስልት አይደለም፡፡ /ቤቶቸ የፖሊሲ ጥያቄዎች ላይ የሚወስኑ ከሆነ በስራ አስፈፃሚ የስልጣን ክልል ውስጥ በመግባት የስልጣን ክፍፍል መርህን በመጣስ ለስልጣናቸው ህገ-መንግስታዊ መሰረት ያጣሉ፡፡
ተጠያቂነት’ የሚለው ቃል የሶስት ንዑስ ሀሳቦች ድምር ውጤት ነው፡፡ እነዚህም ጠያቂ፣ ተጠያቂ እና ጥያቄ ብሎ መከፋፈል ይቻላል፡፡ በአንድ ህገ-መንግስታዊ ስርዓት ውስጥ ተጠያቂነት አለ ለማለት፤
ጠያቂው አካል የቱ ነው?
ተጠያቂው አካል ማን ነው?
መጠየቅ ምንድነው? የመጠየቂያ መንገዱስ?
ብለን ራሳችንን መጠየቅና ለጥያቄዎቹ ምላሽ ማግኘት ይገባናል፡፡ ለጥያቄዎቹ ምላሽ በመሻት የምናደርገው ትንተና በአሁኑ ወቅት በአገራችን ያለውን ህገ መንግስታዊ ስርዓት መሰረት ያደረገ ይሆናል፡፡
የዲሞክራሲ አንደኛው ገጽታ መንግስት ለህዝብ ተጠያቂ የሚሆንበት ስርዓት ነው፡፡ ሆኖም በተግባር ደረጃ ሙሉ በሙሉ ቀጥተኛ ህዝባዊ ተጠያቂነትን ማሳካት የማይቻል በመሆኑ በምርጫ የህዝብ ውክልና የተሰጣቸው እንደራሴዎች ስለህዝቡ ሆነው በመንግስት ላይ ክትትል እና ቁጥጥር ያደርጋሉ፡፡ በአጭር አነጋገር ጠያቂው አካል በተለምዶ ህግ አውጪ ወይም ፓርላማ ተብሎ የሚጠራው ተቋም እንደሆነ እናያለን፡፡ የኢ... ህገ መንግስት መንግስትን የመቆጣጠር እና ተጠያቂነቱን የማረጋገጥ ስልጣንና ግዴታ የህዝብ ተወካዮች /ቤት ስለመሆኑ በማያሻማ አነጋገር አስቀምጦታል፡፡
ጠያቂው ከታወቀ በቀጣይነት የሚነሳው ጥያቄ ተጠያቂ የሚሆነው አካል ማነውየሚለው ይሆናል፡፡ ተጠያቂነት ጠቅለል ባለ መልኩ ሲታይ ከስራ አስፈፃሚው ባሻገር የፓርላማውንና የፍ/ቤቶችን ተጠያቂነት ጭምር የሚወክል ቢሆንም የእነዚህ ተጠያቂነት ከአስተዳደር ህግ የጥናት ወሰን ውጪ በመሆኑ ትኩረታችንን በመንግስት ተጠያቂነት ማለትም በስራ አስፈፃሚው ተጠያቂነት ላይ ብቻ እንገድባለን፡፡
በአገራችን በፌደራል መንግስት ደረጃ የስራ አስፈፃሚነት ስልጣን የተሰጠው ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ለሚኒስትሮች /ቤት እንደመሆኑ የመንግስት ተጠያቂነት የሚኒስትሮችን የነጠላ እና የወል ተጠያቂነት ያመለክታል፡፡ በህዝብ ተመርጠው የአስፈፃሚነት ስልጣን የተሰጣቸው ሚኒስትሮችና ሌሎች የመንግስት /ቤት ባለስልጣናት ለሚያስፈጽሙት ህግና ፖሊሲ የነጠላ ተጠያቂነት እንዲሁም በሚኒስትሮች /ቤት አባልነታቸው (የሚኒስትሮች /ቤት አባል ከሆኑየጋራ ተጠያቂነት አለባቸው፡፡ ይህም ማለት አንድ ሚኒስትር በስሩ ላሉት የአስተዳደር /ቤቶች የስራ አፈፃፀም እንዲሁም ራሱ ለሚመራው ሚኒስትር /ቤት እንቅስቃሴ በግል ቀጥተኛ ተጠያቂነት አለበት፡፡ ከዚህም ባሻገር ሚኒስትሩ በሚኒስትሮች /ቤት አባልነቱ /ቤቱ ለሚወስዳቸው እርምጃዎች የጋራ ተጠያቂነት አለበት፡፡ በኢ... ህገ መንግስት አንቀጽ 72/2/ ግልፅ ሆኖ እንደተደነገገው፤
የሚኒስትሮች ምክር ቤት አባላት በመንግስት ተግባራቸው በጋራ ለሚሰጡት ውሳኔ የጋራ ኃላፊነት አለባቸው፡፡
በመጨረሻም የመጠየቅ ይዘትና ትርጓሜ እንዲሁም የተጠያቂነት መንገዱና ስልቱ ሊዳሰስ የሚገባው ነጥብ ነው፡፡ ለመሆኑ መጠየቅ ማለት ምን ማለት ነው?
መጠየቅ የሚለው ቃል ተጠያቂነትን (Responsibility) እና ኃላፊነትን (Accountability) ያመለክታል፡፡ ተጠያቂ (Respond-ability) መሆን ማለት መግለጫ ወይም ማብራሪያ የመስጠት እንዲሁም ትክክለኛነቱን ማስረዳት ማለት ነው፡፡ ይህም በዋነኛነት በህዝብ ተወካዮች /ቤት ፊት በአካል ቀርቦ ከምክር ቤቱ ለሚነሱ ጥያቄዎች በቂ ምላሽ መስጠት፣ ለምክር ቤቱ ትክክለኛና የተሟላ መረጃ የመስጠት ግዴታን ይጨምራል፡፡
ተጠያቂነት መግለጫ በመስጠት ብቻ አያበቃም፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች ተጠያቂው ለቀረቡለት ጥያቄዎች አሳማኝ እና በቂ ምላሽ ሳይሰጥ ሊቀር ይችላል፡፡ ከዚህም ባሻገር ሆነ ብሎ ወይም በቸልተኝነት ለም/ቤቱ የተሳሳተ መረጃ ሊያቀርብ ወይም የተፈለገውን መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ የማይሆንበት አጋጣሚ ይኖራል፡፡ በእነዚህ ሁሉ ድምር ውጤቶች ምክንያት የተጠያቂው ስህተት እና ድክመት በግልጽ ከታየ ተጠያቂነት በማዕቀብ (sanction) መታገዝ አለበት፡፡
ስለሆነም ሁለተኛው የተጠያቂነት ገጽታ ኃላፊነት የመውሰድ ግዴታ ነው፡፡ ኃላፊነት ሲወሰድ ህገ-ወጥ እርምጃ ወይም ተግባር ከተፈጸመ፣ ህግና ፖሊሲውን የማስፈጸም ድክመትና ቸልተኝነት ከታየ የሚመለከተው ሚኒስትር ወይም ባለስልጣን ስህተቱና ድክመቱ የሚያስከትለውን ውጤት መቀበል ይጠበቅበታል፡፡ ኃላፊነትን የመቀበል ውጤት በገዛ ፈቃድ ስልጣን መልቀቅ ወይም አለፈቃድ ከስልጣን የመወገድ እርምጃ ያስከትላል፡፡
በገዛ ፈቃድ ስልጣን መልቀቅ በብዙ ዲሞክራሲያዊ አገራት የተለመደ ቢሆንም መልካም አስተዳደር ባልሰፈነበት አገር በመንበረ ስልጣን ላይ መጣበቅና ሙጭጭ ማለት በተግባር ይከሰታል፡፡ እዚህ ላይ በገዛ ፈቃዱ ስልጣን መልቀቅ ያለበት ሚኒስትር ኃላፊነት ሳይወስድ ቢቀር ‘አላየሁምአልሰማሁም!’ ቢል የሚከተለው ማዕቀብ ምንድ ነውብሎ መጠየቅ አግባብነት አለው፡፡ በሌላ አነጋገር አንድ ሚኒስትር ግዙፍ ስህተትና ጥፋት መስራቱ ተረጋግጦ እያለ በገዛ ፈቃዱ ስልጣኑን ካልለቀቀ የተወካዮች ምክር ቤት ምን ማድረግ ይችላል?

 

 የኢ... ህገ መንግስት አንቀጽ 55/17/ የም/ቤቱን የመጠየቅና የመመርመር ስልጣን በግልጽ ዕውቅና በመስጠት መውሰድ የሚችላቸውን እርምጃዎች በዝምታ አልፎታል፡፡ ከዚህ አንጻር ግዙፍ ግድፈት የታየበትን ሚኒስቴር ወይም ባለስልጣን ከስልጣኑ ለመሻር የሚችልበት ህገ መንግስታዊ ብቃት የለውም፡፡

WordPress

WELCOME TO MUHAJER SEMAN SURAFEL WEBSITES HOME ON WORDPRESS

This blog is for individuals and private organizations who want to read the FDRE Constitution as well as the interpretations of the Constitution as well as various laws of our country, various proclamations, government-approved directives, teachings and publications. Laws and the Constitution of our country. It is a website where we volunteer to help the public learn about draft laws and interpretations of the constitution

BLOG CATEGORIE'S

ABOUT CONTACT & MAPS

Share This It!